Download this Blogger Template by Clicking Here!

Ad 468 X 60

Tuesday 26 August 2014

Widgets

አዛንና ኢቃም



                                   ትምህርት ቁጥር 1

                                    #አዛንና_ኢቃም

የአዛንና ኢቃም ትርጉሞችና ሸሪዓዊ ድንጋጌዎቻቸው

. የአዛንና የኢቃም ትርጉም፦

አዛን ማለት የዓረብኛ ቋንቋ ትርጉሙ ማሳወቅ ማለት ነው፡፡
አላህ እንዲህ ብሏል፡-
ይህ) ከአላህና ከመልክተኛው በታላቁ ሐጅ ቀን የወጣ ወደ ሰዎች የሚደርስ ማስታወቂያ ነው”(9:3)

ሸሪዓዊ ትርጉሙ፦ በተወሰኑ ዚክሮች የሰላት ወቅት መድረሱን ማሳወቅ ማለት ነው፡፡
ኢቃማ ማለት ደግሞ የዓረብኛ ቋንቋ ትርጉሙ የተቀመጠን ማስነሳት ማለት ሲሆን ሸሪዓዊ ትርጉሙ በሚታወቁ ዚክሮች ለሰላት እንዲቆም የሚደረግ ጥሪ ማለት ነው፡፡

. ሸሪዓዊ ድንጋጌያቸው፦
አዛንና ኢቃም ለአምስት ሰላቶች ወንዶች ላይفرض كفاية” (በተወሰኑ ሰዎች ላይ ብቻ ግዴታ) የሆነ ሲሆን በቂ ሰው ከፈፀመው ግዴታነቱ ከሁሉም ይነሳል፡፡

ሁለተኛ

ትክክለኛ እንዲሆኑ መሟላት ያለባቸው መስፈርቶች
1.
ሙስሊም መሆን፡- ካፊር ቢፈፅማቸው ትክክለኛ አይሆኑም
2.
አእምሮ ጤናማ መሆን፡- ልክ እንደሌሎች አምልኮቶች እብድ በስካር ላይ ያለና ህፃን ቢፈፅማቸው ትክክል አይሆኑም፡፡
3.
ወንድ መሆን፡- ሴት ድምጿ ፈታኝ በመሆኑ አዛን ማድረግ የለባትም፡፡ እንዲሁም ፍናፍንት ከሆነ ወንድነቱ ስለማይታወቅ አዛንና ኢቃም ማድረግ የለበትም፡፡
4.
አዛኑን በሰላት ወቅት ማድረግ፡- ለሱብሂና ለጁምዓ የመጀመሪያዎች አዛን ካልሆነ በቀር የሰላት ወቅት ሳይደርስ አዛን ማድረግ አይፈቀድም፡፡ ኢቃም የሚደረገው ደግሞ ሰላት ውስጥ ለመግባት ሲፈለግ መሆን አለበት፡፡
5.
አዛንና ኢቃም ሲደረግ ቅደም ተከተላቸውን የጠበቀ ተከታታይ የሆኑ ቃላቶች መሆን አለባቸው፡፡ የአደራረጉ ሁኔታ አራተኛው ነጥብ ላይ ይገለፃል፡፡
6.
አዛንና ኢቃም ሸሪዓው በደነገጋቸው ቃላቶችና በዓረብኛ ቋንቋ መደረግ አለባቸው፡፡

                            ትምህርት ቁጥር 2

               #አዛን_አድራጊው_ሊላበሳቸው_የሚወደዱ_ባህሪዎች

1. እውነተኛና ታማኝ ሊሆን ይገባል፡፡ ምክንያቱም ሰዎች ለሰላትና ለፆም የሚመረኮዙት በመሆኑ እንዲህ ካልሆነ በአዛኑ ሊያሳስታቸው ይችላል::
2. አቅመ አዳም የደረሰና አእምሮ ጤናማ መሆን አለበት፡፡ ነገር ግን የሚለይ ህፃን ልጅ አዛን ቢል ትክክል ይሆናል፡፡
3. የሰላት ወቅቶችን የሚያውቅ መሆን አለበት፡፡ ምክንያቱም የመጀመሪዎች መቅቶችን እየተጠባበቀ አዛን ስለሚያደርግ ነው:: የማያውቅ ከሆነ ግን ሊሳሳት ወይም ሊያበላሽ ይችላል::
4. ድምፁ ከፍተኛ ሆኖ ሰዎችን ሊያሰማ የሚችል መሆን አለበት፡፡
5. ከትልቁም ሆነ ከትንሹ ሀደስ የፀዳ መሆን አለበት፡፡
6. ቆሞ ወደ ቂብላ በመዞር አዛን ማድርግ አለበት፡፡
7. ጣቶችን ጆሮው ውስጥ ከትቶ
حي على الصلاة” ሲል ወደ ቀኝ
حي على الفلاح” ሲል ደግሞ ወደ ግራ እየዞረ ማድረግ አለበት፡፡
8. አዛንን ቀስ እያለና ክፍተት እየፈጠረ ኢቃምን ደግሞ እያፋጠነና እያከታተለ ማድግ አለበት፡፡

                             #የአዛንና_የኢቃም_አደራረግ

በሀዲስ ጥቅሶች የተዘገቡ የአዛንና የኢቃም አደራረጐች ብዙ ናቸው፡፡ ከነዚህም ውሰጥ ነብዩ (
) ለአቢ መህዙር የአስተማሩት አደራረግ እንደሚከተለው ነው፡፡
“አሏሁ አክበር አሏሁ አክበር አሏሁ አክበር አሏሁ አክበር፣
አሽሐዱ አንላኢላሃ ኢለሏህ አሽሐዱ አንላኢላሃ ኢለሏህ
አሽሐዱ አነ ሙሐመደ ረሱላሏህ አሽሐዱ አነ ሙሐመደ ረሱላሏህ
ሀየ ዓለ ሰላት ሀየ ዓለ ሰላት
ሀየ ዓለል ፈላህ ሀየ ዓለል ፈላህ
አሏሁ አክበር አሏሁ አክበር
ላኢላሃ ኢለላህ”

                                #የኢቃም_አደርረግ ደግሞ

“ አሏሁ አክበር አሏሁ አክበር፣
አሽሐዱ አንላኢላሃ ኢለሏህ
አሽሐዱ አነ ሙሐመደ ረሱላሏህ
ሀየ ዓለ ሰላት
ሀየ ዓለል ፈላህ
ቀድ ቃመቲ ሰላት ቀድ ቃመቲ ሰላት
አሏሁ አክበር አሏሁ አክበር ላኢላሃ ኢለላህ”
ለዚህ ማሰረጃው አነስ ባስተላለፉት ሀዲስ እንዲህ ብለዋል
“ቢላል አዛን ሲያደርግ ጥንድ ጥንድ እንዲያደርግ ኢቃም ሲያደርግ ደግሞ “ቀድ ቃመቲ ሰላት” ሲቀር ሌሎችን በነጠላ እንዲያደርግ ታዟል፡፡”(ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)
ይህ የአዛንና የኢቃም አደራረግ ቢላል ከነብዩ (
) ሀገሩ ጉዞም ላይ ሲሆን የሚያደርገው በመሆኑ የተወደደ አደራረግ ነው፡፡ አዛን ሲደረግ በተርጂዕ(አዛን ላይ የምስክር ቃሎችን ሲናገር አስቀድሞ ለራሱ ብቻ በሚሰማ መልኩ ካለ በኋላ በመጮህ መድገም ነው፡፡) ኢቃም ደግሞ በጥንድ ቢደረግ ችግር የለውም፡፡ ምክንያቱም እንዲህ አይነቱ ልዩነቶች የተፈቀዱ ናቸው፡፡ የሱብሂ አዛን ላይ “ሀየ አለል ፈላህ” ከተባለ በኋላ “አሰላቱ ኸይሩ ሚነ ነውም” ሁለት ጊዜ ማለት ሱና ነው፡፡ምክንያቱም አቡ መህዙም ባስተላለፉት ሀዲስ ነብዩ () እንዲህ ብለዋል:- “ለሱብሂ ሰላት አዛን ስታደርግ “አሰላቱ ኸይሩ ሚነ ነውም” በል፡፡”
                             ትምህርት ቁጥር 3

              #አዛን_አድማጭ_የሚለውና #ከአዛን_በኋላ_የሚደረግ_ድዓ

አዛን አድማጭ የሚለውና ከአዛን በኋላ የሚደረግ ድዓ
አዛን ሲደረግ የሚያዳምጥ ሰው አዛን አድራጊው የሚለውን ቢል የተወደደ ነው፡፡ ለዚህ ማስረጃው
አቡ ሰዒድ ባስተላለፉት ሀዲስ ነብዩ (
) እንዲህ ብለዋል
“አዛን ስትሰሙ አዛን አድራጊው የሚለውን በሉ፡፡”(ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)
“ሀየ አለ ሰላት” እና “ሀየ ፈለል ፈላህ” ሲል ግን አድማጭ “ላሀውለ ወላ ቁወተ ኢለ ቢላህ” (ከአላህ እገዛ ውጭ ብልሀትም ሆነ አቅም የለም ማለት ነው፡፡) ማለት አለበት፡፡
አዛን አድራጊው የሱብሂ አዛን ውስጥ “አሰላቱ ኸይሩ ሚነ ነውም” ሲልም አድማጭ በተመሳሳይ እራሱ ያለውን ይላል፡፡ ይህን ማድረግ ለአዛን እንጂ ለኢቃም አይፈቀድም፡፡ በመጨረሻም ነብዩ (
) ላይ አላህ ሰላትና ሰላምን እንዲያወርድ ከለመነ በኋላ የሚከተለውን ይላል

اللهم رب هذه الدعوة التامة والصلاة القائمة آتي محمدا الوسيلة والفضيلة وابعثه مقاما محمودا

“አሏሁመ ረበ ሀዚሂ ደዕወቲ ታማህ ወሰላቲል ቃኢማህ አቲ ሙሐመደን አልወሲለተ ወልፈሊላህ ወብዐስሁ መቃመን መህሙዳህ”(ቡኻሪ ዘግበውታል)

ትርጉሙም (ጌታዬ ሆይ የዚህ ሙሉዕ ጥሪ ጌታ ሆይ የቆመው ሰላት ጌታ ሆይ ለሙሐመድ ወሲላንና(ነቢዩ እንዲህ ሲሉ ተርጉመውታል “ጀነት ውስጥ ለአንድ ሰው ብቻ የተወሰነ ልዩ ማዕረግ ነው እኔ እንድሆን እመኛለው”) ብልጫን ለግስ እንዲሁም ምስጉን ማዕረግ ላይ አድርጋቸው፡፡) ማለት ነው

SHARE THIS POST   

  • Facebook
  • Twitter
  • Myspace
  • Google Buzz
  • Reddit
  • Stumnleupon
  • Delicious
  • Digg
  • Technorati
Author: Mohammad
Mohammad is the founder of STC Network which offers Web Services and Online Business Solutions to clients around the globe. Read More →

0 comments: